የአማካይ መስመር ተጫዋቹ ዮሴፍ ዮሐንስ ወደ ቀድሞ ክለቡ የተመለሰበትን ዝውውር አገባዷል።
በዝውውር መስኮት ወሳኝ የሆኑ ተጫዋቾችን እየቀላቀለ የሚገኘው የአሰልጣኝ ሥዩም ከበደው ሲዳማ ቡና ከአብዱራህማን ሙባረክ ፣ ደስታ ዮሐንስ ፣ ፍቅረየሱስ ተወልደብርሃን፣ ብርሀኑ በቀለ እና ጌታነህ ከበደ በመቀጠል ስድስተኛው ፈራሚ ዮሴፍ ዮሐንስ ሆኗል።
ከሀዋሳ ከተማ ወጣት ቡድን ከተገኘ በኋላ በሲዳማ ቡና ፣ አዳማ ከተማ እና የተጠናቀቀውን የውድድር ዘመን ደግሞ በድሬዳዋ ያሳለፈው ተጫዋቹ ከሁለት ዓመታት በኋላ ወደ ቀደመ ክለቡ ሲዳማ በድጋሜ ተመልሷል።
