አዳማ ከተማ አጥቂ አስፈርሟል

አዳማ ከተማ አጥቂ አስፈርሟል

የቅድመ ውድድር ዝግጅታቸውን እየሰሩ የሚገኙት አዳማ ከተማዎች 11ኛ ተጫዋቻቸውን አስፈርመዋል።

በመቀመጫ ከተማቸው የቅድመ ውድድር ዝግጅታቸውን እየሰሩ የሚገኙት አዳማ ከተማዎች በዝውውር ገበያው እስከ አሁን ተክለማርያም ሻንቆ ፣ መላኩ ኤልያስ ፣ ሱራፌል ዐወል ፣ ኤፍሬም ዘካርያስ ፣ ፍቅሩ አለማየሁ ፣ አህመድ ረሺድ ፣ ተስፋሁን ሲሳይ ፣ ሬድዋን ሸሪፍ ፣ አሸናፊ ኤልያስ እና አቡበከር ሻሚልን በይፋ ያስፈረሙ ሲሆን አሁን ደግሞ 11ኛ ፈራሚ በማድረግ አጥቂው ጫላ በንቲን የግላቸው አድርገዋል።

የቀድሞው የነቀምት ከተማ ፣ ሀምበሪቾ ዱራሜ ፣ ቡራዩ ከተማ እና ጅማ አባጅፋር አጥቂ የተጠናቀቀውን የውድድር ዘመን በድሬዳዋ ከተማ ካሳለፈ በኋላ ቀጣዩ መዳረሻው የአሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለው አዳማ ሆኗል።