ደሴ ከተማ በርካታ ተጫዋቾችን ወደ ስብስቡ ቀላቅሏል

ደሴ ከተማ በርካታ ተጫዋቾችን ወደ ስብስቡ ቀላቅሏል

በከፍተኛ ሊጉ የሚሳተፈው ደሴ ከተማ  በርከት ያሉ ተጫዋቾችን በማስፈረም በዝግጅት ላይ ይገኛል።

ደሴ ከተማ ለ2016 የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ውድድር በምድብ ለ የተመደበ ሲሆን በአሰልጣኝ ዳዊት ታደለ እየተመራ ዝግጅቱን በአዳማ ከተማ ማድረግ ከጀመረ ሰንበት ብሏል። ለውድድሩም ይጠቅመኛል ያላቸውን ከፕሪሚየር ሊግ እና ከከፍተኛ ሊግ ወደ 16 የሚጠጉ ተጫዋቾችን የግሉ ማድረግ ችሏል ።

በዚህም የቀድሞው የኮልፌ ክ/ከተማ ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ግብ ጠባቂ እሸቱ ተሾመ ፤ ከዚህ ቀደም ለአውስኮድ ፣ ጅማ አባ ቡና እና ዳሞት ከተማ ሲጫወት የቆየው ግብ ጠባቂ ዘላለም ፀሐይ ፤ በተከላካይ ስፍራ ላይ ደግሞ ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ከተማ ፣ ኢትዮጵያ መድን እና ቡራዩ ከተማ ቆይታ የነበረው ሚፍታህ ዐወል ፤ ለአዳማ ከተማ እና ነጌሌ አርሲ የተጫወተው ብሩክ ቦጋለ ፤ ከዚህ ቀደም ለሰበታ ፣ ለአዳማ እና ለኢትዮ ኤሌክትሪክ የተጫወተው ታፈሰ ሰረካ ፤ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣  በውሃ ሥራዎች ፣ መቻል ተስፋ እና ገላን ከተማ ቆይታ የነበረው ዘሪሁን አብይ እንዲሁም የቀድሞው የዲላ ከተማ እና ጅማ አባ ጅፋር ተጫዋች ዝናው ዘላለም ሆነዋል።

የአማካይ ስፍራ ተጫዋቾችን ስንመለከት ከዚህ በፊት ለሀምበሪቾ ዱራሜ ፣ ነቀምት ከተማ እና ለጅማ አባጅፋር ሲያገለግል የቆየው ዋኩማ ዴንሳ ፤ የቀድሞው የአዳማ ተጫዋች አዲስ ግርማ ፤ ከዚህ በፊት በመቀለ 70 እንደርታ ፣ በለገጣፎ ለገዳዲ ፣ በሀምበሪቾ እና ገላን ከተማ ቆይታ የነበረው በሱፍቃድ ነጋሽ ፤ የቀድሞው የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ እና የኮልፌ ክ/ከተማ ተጫዋች ያሬድ ዓለማየሁ ፤ የቀድሞው የወላይታ ዲቻ ተጫዋች እንድሪስ ሰዒድ ናቸው።

በአጥቂ መስመር ላይ ከዚህ ቀደም ለወረኢሉ የተጫወተው በረከት ወሰን ፤ ከዚህ በፊት በኢትዮ ኤሌክትሪክ ከተስፋው ቡድን እስከ ዋናው ቡድን ያገለገለው ፀጋ ደርቤ ፣ የቀድሞው የሀላባ ከተማ ተጫዋች አቡሽ ደርቤ ከዚህ በፊት ለቤንችማጂ ቡና ፣ ዳሞት ከተማ እና ቡራዩ ከተማ የተጫወተው ሙሉጌታ ካሳሁን ሆነዋል።