ዛሬ የሚደረገው የካፍ ቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ በኢትዮጵያዊያን ዳኞች ይመራል

ዛሬ የሚደረገው የካፍ ቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ በኢትዮጵያዊያን ዳኞች ይመራል

ዛሬ አመሻሽ ሞሮኮ ላይ የሚደረግ የካፍ ቻምፒየንስ ሊግ መርሀግብር በአራት የሀገራችን ዳኞች ይመራል።

የ2024/25 የካፍ ቻምፒየንስ ሊግ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታዎች ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ መደረግ የጀመሩ ሲሆን የመልስ መርሀግብሮችም ከዛሬ ጀምሮ እየተደረጉ ይገኛል። በዛሬው ዕለት 10 ሰዓት ላይ የሞሮኮው አንጋፋ ክለብ ራጃ ካዛብላንካ ከ ኒጀሩ ኤ ኤስ ኤን ኤን የሚያደርጉትን መርሀግብር አራት አለም አቀፍ ኢትዮጵያዊያን ዳኞች እንዲመሩት መመረጣቸውን ሶከር ኢትዮጵያ አረጋግጣለች።

በመሐል ዳኝነት ዶ/ር ኢንተርናሽናል ዳኛ ሀይለየሱስ ባዘዘው ረዳት በመሆን ደግሞ ኢንተርናሽናል ረዳት ዳኞቹ ተመስገን ሳሙኤል እና ይበቃል ደሳለኝ ፣ ኤፍሬም ደበሌ በበኩሉ በመድረኩ የመጀመሪያ ጨዋታውን አራተኛ ዳኛ ሆኖ ተመድቦበታል።