የአሰልጣኞች አስተያየት | ኢትዮ ኤሌክትሪክ 1-0 ባህር ዳር ከተማ

በዕለቱ ቀዳሚ በነበረው መርሃግብር ኢትዮ ኤሌክትሪኮች የውድድር ዘመኑን የመጀመሪያ ድላቸውን ካሳኩበት ጨዋታ መጠናቀቅ በኋላ የሁለቱ ቡድኖች አሰልጣኞች ተከታዩን ሀሳብ ለሶከር ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።

ዘሪሁን ሸንገታ – ኢትዮ ኤሌክትሪክ

“በጠንካራው ጨዋታ ድል ማድረጋችን የማሸነፍ ስነልቦናችንን ከፍ ያደርጋል ፤ በውጤቱ ኮርቻለሁ በልጆቼም በጣም ደስተኛ ብሆንም ከዚህ በላይ ማድረግ እንደሚችሉ አምናለሁ።”

ደግአረግ ይግዛው – ባህር ዳር ከተማ

“በዛሬውን ጨዋታ ቡድናችን ያደረግው እንቅስቃሴ በጠበቅነው ልክ አላገኘነውም ፤ እንደ ቡድን ወርደን ነው የቀረብነው።”

ሙሉውን አስተያየት በዩቲዩብ ገፃችን ለመመልከት – LINK