አርባምንጭ ከተማ ከከፍተኛ ሊግ ተከላካይ አስፈረመ
በአሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ የሚመራው አርባምንጭ ከተማ በዝውውሩ ሁለተኛ ፈራሚውን አግኝቷል። በፕሪምየር ሊጉ ላይ በሁለተኛው ዙር በርካታ ለውጦችን አድርገው ይቀርባሉ ተብለው ከሚጠበቁ ክለቦች መካከል አንዱ የሆነው አርባምንጭ ከተማ እስካሁን የአህመድ ሁሴንን ውል አራዝሞ አበበ ጥላሁንን በአዲስ መልክ ካስፈረመ በኋላ ሌላኛው ፈራሚው በማድረግ ከከፍተኛ ሊጉ ቤንች ማጂ ቡና ዮሐንስ ተስፋዬን የግሉ አድርጓል።Read More →