ከግንቦት ወር መጀመሪያ አንስቶ ሊደረጉ የነበሩት የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታዎች መራዘማቸውን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ከካፍ እንዳረጋገጠ አስታውቋል። “በሞሮኮ አዘጋጅነት የሚካሄደው የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች መራዘማቸውን ካፍ አስታወቀ። ግንቦት 30/2013 የመጀመሪያ ጨዋታውን ከዩጋንዳ አቻው ለመጫወት በካፍ አካዳሚ ዝግጅት ላይ የሚገኘው የሉሲዎቹ ስብስብ በቀጣይ ዓመት በጥቅምት ወር ጨዋታውን እንደሚያደርግ ታውቋል።Read More →

በሞሮኮ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ሴቶች ዋንጫ ማጣርያ ዩጋንዳን ግንቦት መጨረሻ ላይ የሚገጥሙት ሉሲዎቹ አሰልጣኝ ብርሃኑ ግዛው ለ30 ተጫዋቾች ጥሪ አድርገዋል። አመዛኞቹ ተጫዋቾች ባለፈው ወር ደቡብ ሱዳንን የገጠመው ስብስብ አካል የነበሩ ሲሆን አስራ አንድ አዳዲስ ተጫዋቾች ካለፈው ምርጫ ለውጥ የተደረገባቸው ናቸው። ቡድኑ ከእሁድ ጀምሮ በካፍ አካዳሚ ዝግጅት እንደሚጀምር ይጠበቃል።  ዝርዝር ግብRead More →